የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን በችግኝ ተከላ እና እንክብካቤ ላይ ላቅ ያለ ተሳትፎ ያደረጉ ተቋማት የእዉቅና ሽልማት ሰጠ;;
ችግኞች ተተክለዉ ዛፍ እስከሚሆኑ ድረስ እንደ ህፃን ልጂ እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋል ፡፡
ከዚህ አንፃር ባለፈዉ ክረምት ወራት ችግኞችን ተክለዉ እንክብካቤ ያደረጉ ዉሃ ያጠጡ የአረም ኩትኳቶ እና ነቀላ ያደረጉ ችግኞችን ከሰዉ እና ከእንስሳት ንክኪ የጠበቁ ተቋማት ኮሚሽን መስሪያ ቤቱ የእዉቅና ሽልማት ሰጥቷል፡፡
የእዉቅና ሽልማት ከተሰጣቸዉ ተቋማት መካከል ፕላንና ልማት ኮሚሽን ፤ የኢትዩጽያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲቲዩት ፤ የኢትዩጽያ ስኳር ኮርፖሬሽን እና መቶ ሀያ አንድ ተቋማት እንደ ደረጃቸዉ ባደረጉት ክትትል እና የእንክብካቤ ስራ የችግኞችን የጽድቀት መጠን ከ 50 % እስከ 80 % ማድረስ ችለዋል፡፡
በቀጣይም ሌሎች ተቋማት የተከሉትን ችግኝ የመንከባከብ ኃላፊነታቸዉን በተገቢዉ ሁኔታ መወጣት እንዳለባቸዉ እና የእንክብካቤዉን ስራ በተሳካ ሁኔታ ያከናወኑ ተቋማትም ቀጣይነት ባለዉ መልኩ የተሻለ ስራ መስራት እንዳለባቸዉ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሲሳይ ጌታቸዉ ተናግረዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *